father
ጽድቅንና ፍርድን በማድረግ የእግዚአብሔርን መንገድ ይጠብቁ ዘንድ ልጆቹንና ከእርሱ በኋላ ቤቱን እንዲያዝዝ አውቃለሁና፤ ይህም እግዚአብሔር በአብርሃም ላይ የተናገረውን ነገር ሁሉ ያመጣ ዘንድ ነው።
ኦሪት ዘፍጥረት 18 : 19
ስለዚህ ሰው አባቱንና እናቱን ይተዋል፥ በሚስቱም ይጣበቃል፤ ሁለቱም አንድ ሥጋ ይሆናሉ።
ኦሪት ዘፍጥረት 2 : 24
አባትህንና እናትህን አክብር፤ እግዚአብሔር አምላክህ በሚሰጥህ ምድር ዕድሜህ እንዲረዝም።
ኦሪት ዘጸአት 20 : 12
እግዚአብሔርም በፊቱ አልፎ። እግዚአብሔር፥ እግዚአብሔር መሐሪ፥ ሞገስ ያለው፥ ታጋሽም፥ ባለ ብዙ ቸርነትና እውነት፥
ኦሪት ዘጸአት 34 : 6
ሙሴም ለሕዝቡ። አትፍሩ፥ ዛሬ የምታዩአቸውን ግብፃውያንን ለዘላለም አታዩአቸውምና ቁሙ፥ ዛሬ ለእናንተ የሚያደርጋትን የእግዚአብሔርን ማዳን እዩ።
ኦሪት ዘጸአት 14 : 13
እግዚአብሔር ይባርክህ፥ ይጠብቅህም፤
ኦሪት ዘኍልቍ 6 : 24
እኔም ዛሬ አንተን የማዝዘውን ይህን ቃል በልብህ ያዝ።
ኦሪት ዘዳግም 6 : 6
ወደዚህም ስፋራ እስክትመጡ ድረስ በሄዳችሁበት መንገድ ሁሉ፥ ሰው ልጁን እንዲሸከም አምላክህ እግዚአብሔር እንደተሸከመህ አንተ አይተሃል።
ኦሪት ዘዳግም 1 : 31
እኔም አልኋችሁ። አትደንግጡ፥ ከእነርሱም አትፍሩ፤
ኦሪት ዘዳግም 1 : 29
፤
ኦሪት ዘዳግም 4 : 9

