wisdom

እግዚአብሔር የመንገዱ መጀመሪያ አደረገኝ፥ በቀድሞ ሥራው መጀመሪያ።

መጽሐፈ ምሳሌ 8 : 22

ወዳጁን የሚንቅ እርሱ አእምሮ የጐደለው ነው፤ አስተዋይ ግን ዝም ይላል።

መጽሐፈ ምሳሌ 11 : 12

ጥበብን የሚያገኝ ሰው ምስጉን ነው፥ ማስተዋልንም ገንዘቡ የሚያደርግ፤

መጽሐፈ ምሳሌ 3 : 13

አትተዋት፥ ትደግፍህማለች፤ ውደዳት፥ ትጠብቅህማለች።

መጽሐፈ ምሳሌ 4 : 6

ወደ ዘለፋዬ ተመለሱ፤ እነሆ፥ መንፈሴን አፈስስላችኋለሁ፤ ቃሌን አስተምራችኋለሁ።

መጽሐፈ ምሳሌ 1 : 23

የዚያን ጊዜ ይጠሩኛል፥ እኔ ግን አልመልስም፤ ተግተው ይሹኛል፥ ነገር ግን አያገኙኝም።

መጽሐፈ ምሳሌ 1 : 28

ዘመንህ በእኔ ይበዛልና፥ የሕይወትህም ዕድሜ ይጨመርልሃልና።

መጽሐፈ ምሳሌ 9 : 11

ጥበብ ከቀይ ዕንቍ ትበልጣለችና የከበረ ነገር ሁሉ አይተካከላትም።

መጽሐፈ ምሳሌ 8 : 11

ከፍ ከፍ አድርጋት፥ እርስዋም ከፍ ከፍ ታደርግሃለች፤ ብታቅፋትም ታከብርሃለች።

መጽሐፈ ምሳሌ 4 : 8

እኔ ጥበብ በብልሃት ተቀምጫለሁ፥ እውቀትንም ጥንቃቄንም አግኝቻለሁ።

መጽሐፈ ምሳሌ 8 : 12